በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
ይህ ማህበር 'ማህበረ ኪዳነ ምህረት' መሰረቱን በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያደረገ ሲሆን አላማውም:
1 ግልጽ እና ተዓማኒነት ያለው የቤተክርስትያን አገልግሎት ፤
2 በአጓጉል ምክንያት ከቤተክርስቲያን መባንና አስራትን ለማያስገቡ ምዕመናን ተጨባጭ መረጃዎችን በማቅረብ እና ሁሉም የማህበሩ አባላት ሊያጣሩ በሚችሉበት አሰራር የጠፉትን ወደ ቤተክርስቲያናችን ስርዐት መመለስ፤
3 በ3 የማይተዋወቁ ነገር ግን በትልቅ ጥንቃቄ በተመረጡ ክርስቲያኖች ስም በተከፈተ የባንክ ቁጥር ሚስጥራዊነቱ እንዲሁም ግልፀኝነቱ በተጠበቀ ሁኔታ አስራት በኩራትን መሰብሰብ፤
4 በተሰበሰበው መባ በአመት 1፣2 ወይም3 ጊዜ እንደ አቅማችን የሚወሰን ሲሆን የተረሱ፣ አስታዋሽ ያጡ አብያተ ክርስቲያናትን ማሳደስ እንዲሁም የአብነት ትምህርት እንዲስፋፋ ማገዝ፤
5 አቅማችን ሲጨምር አብያተ ክርስቲያናትን ማነፅ እና ለህብረተሰቡ ማበርከት ናቸው።
አነሳስቶ ላስጀመረን አስጀምሮም ላስፈፀመን ለልዑል እግዚአብሔር ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ምስጋና ይገባል ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን።
Shared 11 months ago
57 views
Shared 2 years ago
6 views
Shared 2 years ago
36 views
Shared 4 years ago
96 views
Shared 4 years ago
947 views
Shared 5 years ago
260 views
Shared 5 years ago
528 views