ማሕበረ ኪዳነ ምህረት_Mahebere Kidane Meheret_Official

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

ይህ ማህበር 'ማህበረ ኪዳነ ምህረት' መሰረቱን በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያደረገ ሲሆን አላማውም:

1 ግልጽ እና ተዓማኒነት ያለው የቤተክርስትያን አገልግሎት ፤

2 በአጓጉል ምክንያት ከቤተክርስቲያን መባንና አስራትን ለማያስገቡ ምዕመናን ተጨባጭ መረጃዎችን በማቅረብ እና ሁሉም የማህበሩ አባላት ሊያጣሩ በሚችሉበት አሰራር የጠፉትን ወደ ቤተክርስቲያናችን ስርዐት መመለስ፤

3 በ3 የማይተዋወቁ ነገር ግን በትልቅ ጥንቃቄ በተመረጡ ክርስቲያኖች ስም በተከፈተ የባንክ ቁጥር ሚስጥራዊነቱ እንዲሁም ግልፀኝነቱ በተጠበቀ ሁኔታ አስራት በኩራትን መሰብሰብ፤

4 በተሰበሰበው መባ በአመት 1፣2 ወይም3 ጊዜ እንደ አቅማችን የሚወሰን ሲሆን የተረሱ፣ አስታዋሽ ያጡ አብያተ ክርስቲያናትን ማሳደስ እንዲሁም የአብነት ትምህርት እንዲስፋፋ ማገዝ፤

5 አቅማችን ሲጨምር አብያተ ክርስቲያናትን ማነፅ እና ለህብረተሰቡ ማበርከት ናቸው።

አነሳስቶ ላስጀመረን አስጀምሮም ላስፈፀመን ለልዑል እግዚአብሔር ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ምስጋና ይገባል ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን።