EBC

አየር መንገዱ 30ኛውን ቦይንግ ድሪምላይነር አውሮፕላን ተረከበ
*******
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ አዲስ ቦይንግ 787- 8 ድሪምላይነር አውሮፕላን ዛሬ ተረክቧል፡፡
አየር መንገዱ የተረከበው አዲሱ አውሮፕላን በአንድ ጊዜ 213 መንገደኞችን ማጓጓዝ ያስችላል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲሱን አውሮፕላን መረከቡ፤ በባለቤትነት የያዛቸውን የቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላኖች ቁጥር 30 አድርሶታል፡፡
አየር መንገዱ አዲሱን አውሮፕላን መረከቡ፤ አፍሪካን ከዓለም በማገናኘት እየሰጠ ያለውን ምቹና ጥራት ያለው አገልግሎት አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚያስችለው ገልጿል፡፡
አዲሱ ቦይንግ 787- 8 ድሪምላይነር አውሮፕላን እጅግ ዘመናዊ ሲሆን፣ ከሌሎች አውሮፕላኖች አንፃር አነስተኛ የድምፅ ብክለት ያለውና ይበልጥ አስተማማኝ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
በተጨማሪም አውሮፕላኑ ሰፊ የመስኮት እይታ ያለው በመሆኑ፤ መንገደኞች በረራ ሲያደርጉ የተሻለ ምቾት እንዲኖራቸው የሚረዳ መሆኑ ተገልጿል።

4 days ago | [YT] | 268