ልዳ ሚዲያ - Leda Media

#አቡነ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ

#በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በፃድቁ ስም ለምናመሰግንበት ለፃድቁ አቡነ #እስትንፋሰ_ክርስቶስ ዓመታዊ የልደት መታሠቢያ ክብረ በዓል እንኳን አደረሰን

#እግዚአብሔር በፃድቁ እንደተገለጠ እወቁ" መዝ፤4፣3

#አቡነ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ አባታቸው #መላከ እናታቸው #ወለተ_ማርያም ይባላሉ የተወለዱበት ልዩ ቦታው ወሎ ክፍለ ሀገር ዳውንት ነው በተወለዱ ዕለት ተነስተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ በአንድነት በሶስትነት ለሚመሰገን ለአጋእዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ #ስብሐት_ለአብ #ስብሐት_ለወልድ #ስብሐት_ለመንፈስ_ቅዱስ ብለው አመስግነዋል

የስማቸው ትርጓሜ #የአብ_የወልድ_የመንፈስ_ቅዱስ እስትንፋስ አንድም #የክርስቶስ_እስትንፋስ ማለት ነው ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸውና በመንገዳቸው ሁሉ እየመራቸው ነው ያደጉት #መንፈስ_ቅዱስ ልቦናቸውን ብሩህ አድርጎላቸው በ5 ዓመታቸው የቅዱሳት መጽሐፍት ቃላትን ብሉያትንና ሐዲሳትን ድርሳናትንም ጠንቅቀው ዐውቀዋል

በተወለዱ በ14 ዓመታቸው ወደ #አቡነ_ኢየሱስ ሞዐ ደብረ ሐይቅ ገዳም ሄደው ከባሕር ዳር ቆመው የሙሴን ጸሎት ወደ #እግዚአብሔር በፀለዩ ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ባህሩን አሻግሯቸው ወደ ቤተክርስቲያን ገብተዋል

ሦስት ዓመትም በኃይቅ ገዳም ለመነኮሳት እንጨት በመልቀምና ውሃን በመቅዳት #ለአባቶች መነኮሳት ምግብ ሊሆናቸው ከባህር ውስጥ አሳን በማውጣት አገልግለዋል

አባታችን #እስትንፋሰ_ክርስቶስ 40 መዓልትና 40 ሌሊት ከፆሙ በኋላ ምንም እህል ሳይቀምሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስቀድሞ #ለሙሴ በደብረ ሲና እንደሰጠው ለአባታችንም ወደ እርሳቸው መጥቶ ዓሥሩን ቃላተ ኦሪትና ስድስቱን ቃላተ ወንጌል በውስጣቸው የተጻፈባቸው ሁለት ጽላቶችን ሰጥቷቸዋል

አቡነ #እስትንፋሰ_ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን ከሠሩ በኋላ ዕለቱን ስንዴ ዘርተው ወይን ተክለው ጽድን ወይራንና ግራርን ተክለው በአንዲት ቀን #ለቤተ_ክርስቲያን አገልግሎት ዕለቱን አድርሰዋል ስንዴውን ለመስዋዕት ወይኑን ለቁርባን በታምራት አድርሰዋል

አባታችን በጸሎት ላይ እንዳሉ መልአኩ #ቅዱስ_ሚካኤል ተልኮ መጥቶ አባታችንን በደመና ጭኖ ወስዶ ከጌታችን ከአምላካችን ከመድኃኒታችን #ከኢየሱስ_ክርስቶስ ፊት አቆማቸው

ጌታም #በቅዱሳኖቹ ሁሉ እንዲባረኩ ካደረጋቸው በኋላ መልአኩን ወደ ተወለድኩባትና ወደ ኖርኩባት ቦታ ወደ ኢየሩሳሌም አድርሰው ብሎት ኢየሩሳሌምን አሳልሞ ሀገራችን መልሶ አምጥቷቸዋል ሁሉንም #የኢትዮጵያን ቅዱሳት ገዳማትንም ተሳልመዋል

የአባታችን #የፃድቁ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ ፀሎትና ቃል ኪዳን ከኛ ጋር ይሁን #የአበዉ_ነብያት ምልጃና ፀሎት ከኛ ጋር ይሁን "አሜን"

#አቡነ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ
#ልዳ_ሚዲያ
#ቤተ_ልዳ_ሚዲያ

youtube.com/@Ledamedia
t.me/+80Qf0_Q0RNZiYWE0
www.facebook.com/mogesabeje94?mibextid=ZbWKwL

3 days ago | [YT] | 273