EBC

ግብርና ሚኒስቴር 258 መኪኖች እና 1 ሺህ 830 የሞተር ብስክሌቶችን ለክልሎች አበረከተ
***************
ግብርና ሚኒስቴር ለምግብ ሥርዓት ማጠናከርያ ፕሮግራም የሚሆኑ 258 መኪናዎችን እና 1 ሺህ 830 የሞተር ብስክሌቶችን ዛሬ ለክልሎች አስረክቧል።
‎ተሽከርካሪዎቹ በተለይም በገጠሩ አካባቢ ዝቅተኛ አቅም ያላቸው ወጣቶች፣ ሴቶች፣ አርሶ እና አርብቶ አደሮች የምግብ ሥርዓት እንዲሻሻል የሚሰሩ ባለሙያዎችን እና የላቦራቶሪ ቁሶችን ለማጓጓዝ እንደሚውሉ በርክክቡ ወቅት ተገልጿል።
‎ሚኒስቴሩ ከዚህ በተጨማሪ የአየር ንብረትን ለሚቋቋም የስንዴ እሴት ሰንሰለት ፕሮግራም 9 መኪኖች፣ 24 የሞተር ብስክሌቶች፣ የውኃ መሳቢያ ሞተር እንዲሁም 100 የመለዋወጫ ዕቃዎችን የያዙ ሳጥኖችን ለክልሎች አስረክቧል።
‎ይህም በኢትዮጵያ የተጀመረውን የበጋ መስኖ ልማትን ይበልጥ ለማስፋፋት እንደሚያግዙ ነው የተገለፀው።
‎የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት፤ ለሁለቱም ፕሮግራሞች ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ የወጣባቸው ድጋፍ ለክልሎች ተደርጓል።
‌‎ተሽከርካሪዎቹ ኢትዮጵያ የያዘችውን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራም ለማሳካት አጋዥ መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ድጋፉ ከልማት አጋሮች በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እንደቀረበ ጠቁመዋል።‎
በባዬ ሙላት
#ebcdotstream #EBC #Ethiopia

3 days ago | [YT] | 386