EBC

ኢትዮጵያ እና ሮማኒያ ያላቸውን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማሳደግ መከሩ
*******************
በቡካሬስት በተካሄደው የኢትዮጵያ-ሮማኒያ የንግድ ፎረም ላይ በስዊዘርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር እና በጄኔቫ የተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ፀጋአብ ክበበው የተመራ ልዑካን ቡድን ተሳትፏል።
በፎረሙ ሮማኒያ ከኢትዮጵያ ጋር የኢኮኖሚ እና የኢንቨስትመንት ዘርፎች ያላችትን ትብብርን ለማስፋት ያላትን ፍላጎት CIB ፕሬዝዳንት ሚስተር ኢዩሊዩ ስቶክሎሳ ሮሳ አስታውቀዋል።
አምባሳደር ፀጋብ በበኩላቸው የኢትዮጵያን የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የቱሪዝም እድሎችን ለተሳታፊዎች ያቀረቡ ሲሆን በኢትዮጵያ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ዘርፎች፣ የተደረጉ ማሻሻያዎችን እና የኢትዮጵያን እያደገ የመጣው የኢኮኖሚ አቅም አብራርተዋል።
በንግድ ፎረሙ ላይ ከሮማኒያ በኩል ፖሊሲ አውጪዎች፣ የንግድ ባለቤቶችን እና ባለሀብቶች ተሳታፊ ሲሆኑ በኢንቨስትመንት ማዕቀፎች፣ በዘርፉ ተስፋዎች እና እድሎች ዙሪያም ውይይት አድርገዋል።

2 days ago | [YT] | 265